ቀን 10/4/2015

ለሚመለከተዉ ሁሉ

የተሰረዘ የሙያ ፈቃድ ምዝገባ የምስክር ወረቀትን ይመለከታል፡፡

ከኢትዮጵያ ሒሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ የሙያ ፈቃድ የምዝገባ የምስክር ወረቀት የወሰደ ማንኛውም የሒሳብ/የኦዲት ባለሙያ የምስክር ወረቀቱን ማሳደስ ከሚገባው ጊዜ ጀምሮ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ካላሳደሰ በሒሳብ እና ኦዲት ባለሙያዎች ፍቃድ አሰጣጥ እና የሒሳብ ሙያ ማኅበራት ምዝገባ መመሪያ ቁጥር 805/2013 አንቀጽ 6(4) መሠረት የምዝገባ የምስክር ወረቀቱ እንደሚሰረዝ ተደንግጓል፡፡ በዚህም መሰረት፡-

1ኛ. ዳግም ደሳለኝ ገደቡ የተፈቀደለት የሂሳብ አዋቂ ድርጅት የምዝገባ ምስክር ወረቀት ቁጥር ACF-00374 እና

2ኛ. ፍቅሩ በቀለ አበበ የተፈቀደለት የሂሳብ አዋቂ ድርጅት የምዝገባ ምስክር ወረቀት ቁጥር ACF00055 የምስክር ወረቀታቸውን ሳያስድሱ አንድ ዓመት ያለፋቸው በመሆኑ ከ ነሐሴ 28/2014 ጀምሮ የምዝገባ የምስክር ወረቀታቸው የተሰረዘ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

ስለሆነም በተጠቀሱት የሒሳብ አዋቂ ድርጅቶች ስም የሒሳብ ሥራ ተሰርቶ ቢገኝ ተቀባይነት የሌለው መሆኑን እናሳስባለን፡፡

 

የኢትዮጵያ ሒሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ